ወደ አዲስ አበባ ንግድ ሥራዎች ድርጅት እንኳን ደህና መጡ፤ የገበያ መረጋጋት እና የአቅርቦት ዋስትና አጋርዎ
ከዘመናዊ የንግድ አሰራር እስከ ጥራት ያለው የአቅርቦት ሰንሰለት አስተዳደር፤ የከተማዋን ነዋሪዎች ፍላጎት መሰረት ያደረጉ እና ለላቀ ውጤት የተለሙ አገልግሎቶችን እናቀርባለን።
የእኛ ታሪክ
የንግድ እና አቅርቦት አገልግሎት ሙያዊ ብቃት ታማኝነት/ጥንቃቄ
የአዲስ አበባ የንግድ ሥራዎች ድርጅት በመነሻ ካፒታል ብር 7.25 ቢሊየን ሐምሌ 15/2015 ዓ/ም በደንብ ቁጥር 152 ተመሰረት፡፡ ድርጅቱ ለከተማ አስተዳደር ሸማቹ ህብረተሰብ የግብርና፣ የኢንዱስትሪ ምርቶችን እና የንግድ እቃዎችን በቀጥታ ከአምራቹ ጋራ የገበያ ትስስር በመፍጠር በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ አገልግሎት እንዲሰጥ የተቋቋመ ድርጅት ነ፡፡ በመጀመሪያ 1 አመት ጊዜ ውስጥ ወደ ብር 85,226,825.22 ብር በላይ ያልተጣራ ትርፍ ያገኘ ሲሆን ድርጅቱ ከከተማ አስተዳደሩ በተሰጠው ድጋፍ ቢሮና መጋዘን ያለው ሲሆን ለድጋፍና ክትትልም ምቹ ስፍራ ላይ ይገኛል፡፡ ድርጅቱ በደንብ ቁጥር 152/2015 ዓ.ም ቢቋቋምም ወደ ስራ የገባው ሚያዝያ 2016 ዓ.ም ነው፡፡ ድርጀቱ የመጀመሪያ ስራ አሰኪያጅ በሆኑት በአቶ መስፍን አሰፋ እየተመራ የገኛል፡፡
2
አመታት የአገልግሎት ዘመን
500K
በመላው አዲስ አበባ ያሉ ደንበኞቻችን
642
በአዲስ አበባ የተከናወኑ ተግባራት
የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደታችን
መሰረታዊ አገልግሎቶቻችንን የሚያገኙባቸው ቅደም ተከተሎች
1. ምዝገባ እና ጥያቄ
ተጠቃሚዎች የሚያስፈልጓቸውን መሰረታዊ ሸቀጦች ወይም ተቋማዊ አገልግሎቶች በመለየት በአካል በቅርንጫፎቻችን በመገኘት ወይም በድረ-ገጻችን አማካኝነት ጥያቄያቸውን ያቀርባሉ። በዚህ ደረጃ አስፈላጊው መረጃ ተሰብስቦ ለቀጣይ ዝግጅት ዝግጁ ይደረጋል።
2. ማረጋገጥ እና ዝግጅት
የቀረቡ ጥያቄዎች በድርጅታችን ባለሙያዎች አማካኝነት ፈጣን ምላሽ ያገኛሉ። የአሰራር ሂደታችን ግልጽነትን እና ተጠያቂነትን የተከተለ ሲሆን፣ ምርቶች በጥራት እና በብዛት ተለይተው ለስርጭት እንዲዘጋጁ ይደረጋል።
3. ስርጭት እና አቅርቦት
በመጨረሻም ጥራት ያላቸው ምርቶች በተመጣጣኝ የገበያ ዋጋ ለነዋሪዎች፣ ለሸማች ማህበራት ወይም ለተቋማት ይሰራጫሉ። ምርቶቹ በሁሉም የከተማዋ ክፍለ ከተሞች በሚገኙ ማእከላቶቻችን አማካኝነት ለህዝብ ተደራሽ ይሆናሉ።
ዋናው ግባችን
ተልዕኮአችን
የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶችን ከሃገር ውስጥና ከውጭ ሃገራት ገዝቶ በማቅረብ፣ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ በማምረት፣ በማስመረት፣ ክምችት በመያዝ እና በከተማዋ ለሚገኙ የመሰረታዊ ሸማች ህብረት ስራ ማህበራት፣ ለአገልግሎት ሰጭ ተቋማት እና ለሸማቹ ህብረተሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ በማሰራጨት ገበያ ማረጋጋት ነው፡፡
ወደፊት የሚታዩ እቅዶች
ራዕያችን
በ2022 ዓ.ም በሀገሪቱ አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም ሰፊ የገበያ ድርሻ ካላቸው ትርፋማ የልማት ድርጅቶች መካከል ግንባር ቀደም ሆኖ ማየት፤
ለማህበረሰባችን መመለስ
የማህበረሰብ ተሳትፎ
ድርጅታችን በተለያዩ ተግባራት ማህበረሰቡን መደገፍ እና ለወገኑ የሚተርፍ ስራ መስራት ትልቅ እሴቱ እንደሆነ ያምናል። በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎችን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ የአቅርቦት ድጋፎችን በማመቻቸትም ሆነ የተለያዩ ማህበራዊ ፕሮጀክቶችን በመደገፍ፣ በከተማችን ነዋሪዎች ህይወት ላይ አዎንታዊ ተፅእኖ ለመፍጠር በቁርጠኝነት እንሰራለን።
አስተማማኝ እና ተመጣጣኝ የገበያ አቅርቦት ለማግኘት ዝግጁ ነዎት ?
ስለ ምርቶቻችን እና አገልግሎቶቻችን ዝርዝር መረጃ ለማግኘት ዛሬውኑ ያግኙን።
